የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ባሕሩ ጥላሁን ለትውልደ ኢትዮጵያዊው የካናዳ ብሔራዊ ቡድን ተጫዋች አሊ አህመድ ወሎ ሰፈር የሚኘው የፌዴሬሽኑ ጽ/ቤት አስጎብኝተዋል፡፡

ዋና ሥራ አስፈፃሚው በጉብኝቱ ወቅት ከአሊ አህመድ ጋር ባደረጉት ቆይታ ኢትዮጵያ በአፍሪካ እግር ኳስ ላይ ስለተጫወተችው ጉልህ ሚና ፤ የአፍሪካ ዋንጫ እና ካፍን ከመመስረት አንስቶ ውድድሩን በማስተናገድ እና ዋንጫ በማንሳት የነበራትን ታሪክ፣ በኢ/እ/ፌ በዋና ፀሐፊነት እንዲሁም የካፍ ኘሬዝዳንትነት ለረጅም ዓመት የመሩት የአፍሪካ እግር ኳስ አባት ክቡር አቶ ይድነቃቸው ተሰማ በካፍ ላይ የነበራቸው ታላቅ አበርክቶ ምን እንደነበረ እንዲሁም አሁን ካፍ ለያዘው ቅርፅ የነበራቸውን ወሳኝ ሚና አስረድተዋል።

ኢትዮጵያውያን እግር ኳስ ተጫዋቾችን በተመለተ ሀገራችን የተሰጥኦ ችግር እንደሌለባትና በይበልጥ ደሞ ትውልደ ኢትዮጵያውያን ለሀገራቸው የሚጫወቱበትን ሁኔታ በተመለከተ አሊ ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ተጫዋች የመሆን እድሉ ባይገጥመውም ጥሩ ደጋፊ በመሆን ዲያስፖራ ኢንተግሬሽን ኘሮግራምን እንደ ሀገር መዘርጋት እንዲቻል ሌሎች ከኢትዮጵያ ውጪ የሚጫወቱ ተጫዋቾችን የማነሳሳት ሥራ የመስራት ከፍተኛ ሚና ሊኖረው እንደሚገባ ገልፀዋል፡፡  

አሊ አህመድ  በትውልደ ኢትዮጵያዊያን ኢንተግሬሽን ኘሮግራም ላይ የበኩሉን አስተዋጽኦ ለማድረግ እና በርካታ ባለተሰጥኦ ኢትዮጵያን ተጫዋቾች በውጪ ሀገር እንደሚገኙ ገልጾ በእዚህም አብሮ ለመሥራት ዝግጁ መሆኑን አሳውቋል። እንዲሁም የብሔራዊ ቡድናችን ደጋፊ መሆኑንም ገልፆል። 

አሊ አህመድ በኢትዮጵያ ቆይታው የደራርቱ ቱሉ ስፖርት አካዳሚን የጎበኘ ሲሆን በዛሬው ዕለት በኢትዮጵያ የነበረውን ቆይታውን አጠናቆ ለሊት ወደ እንግሊዝ ኖርዊች ይጓዛል።

Facebooktwitterlinkedinyoutubetumblrinstagramflickrfoursquaremail
Facebooktwitterredditpinterestlinkedintumblrmail

By admin

Hello, dear. I am Wosenseged Mersha Demissie. Author, Journalist, and Sociological Criticism. He has worked in several media in Ethiopia and foreign media also. I have come to my country, Ethiopia, from abroad, and for the past eight years, I have been giving political analysis and writing in magazines, newspapers, and televisions on all the free press in Ethiopia. I have six books that I wrote and published during my stay abroad and after I came back to my country and are on the market. Above all, I feel spiritual satisfaction for coming from a developed country and working in a country where there is no freedom of the press. I have sacrificed a lot in this profession. Imprisonment, abuse—I was crushed economically. I have been living separately from my family for many years, but I am happy and proud of my career to be a voice for the voiceless people of Ethiopia, whom I love and respect by working in the press without payment. After leaving my country and returning to my country, Growing up in Arat Kilo, YMCA, I was exposed to various sports. I know many sports. I have worked as a referee, player, and tournament organizer. As a result, I have worked as a sports editor on radio, television, and newspapers for many years. I have worked alongside other media outlets for more than 20 years by preparing and publishing my own sports newspaper called San George.I have traveled to many countries, including Europe, the Far East, Asia, Oceania, and Africa, and have been present at many competitions, including athletics.This is because I have this love for sports. I have reopened this media outlet for sports. In addition to this, I have worked for the past 30 years. May God protect Ethiopia and its people and give peace and love to our world. Thank you anyway. Wosenseged Mersha Demissie Author, Journalist, Sociological Criticism

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *