
አርሰናል ከክርስቲያን ኮፋኔ ወኪሎች ጋር እየተነጋገረ ነው ተብሏል። ነገር ግን የባየር ሊቨርኩሰንን አጥቂ ለማስፈረም ከኒውካስል ጋር የሚደረገውን ፉክክር በልጦ መገኘት ሊኖርበት ይችላል።
ኮፋኔ ባለፈው የውድድር ዘመን ከአልባሴቴ ወደ ሊቨርኩሰን ጋር በ5.25 ሚሊዮን ዩሮ (4.5 ሚሊዮን ፓውንድ) ስምምነት ነበር ክለቡን የተቀላቀለው፤በቡንደስሊጋው የመጀመሪያ የውድድር ዘመን አስደናቂ የሆነ የመጀመሪያ ጊዜን አሳልፏል። በመጀመሪያዎቹ 29 ጨዋታዎች ሰባት ጎሎችንና አራት ግብ የሆኑ ኳሶችን አመቻች አቀብሏል።
የ19 ዓመቱ ተጫዋች በቻምፒዮንስ ሊግ ላይም ከፍተኛ ተጽዕኖ አሳድሯል፣ በተለይም በመጋቢት ወር ሊቨርኩሰን በአርሰናል በተሸነፈበት የመጨረሻ 16 ጨዋታ ላይ ድንቅ ብቃት አሳይቶ ነበር።

ከዚያን ጊዜ ጀምሮ የኮፋኔ የወደፊት ዕጣ ፈንታ ከፍተኛ ግምት የሚሰጠው ተጨዋች ሆኖ ሰንብቷል፤ የአጥቂው ውስጣዊ ስሜት በበጋ ወቅት ከፍተኛ ገንዘብ ሊያስገኝ ይችላል ለሚለው ወሬ ብዙም አስተዋጽኦ አላበረከተም፣ ወኪሉ ኤሪክ ዴፖሎ ለዴይሊ ስለ አርሰናል ክለብ ተጨዋቹን እንደሚፈልገው ለተጠየቀው ጥያቄ በሰጠው አስተያየት «አሰልጣኙ [ማይክል አርቴታ] በጣም ይወደዋል» ሲል ለዴይሊ አርሰናል ተናግሯል።
ዴፖሎ ሌሎች ክለቦች በኮፋኔ ላይ ፍላጎት እንዳላቸው በተመለከተ ለተጠየቀው ጥያቄ ሲመልስ «ቼልሲ፣ ኒውካስትል፣ ኤቨርተን፣ ብሬንትፎርድ፣ ባርሴሎናና ባየርን ሙኒክም ይፈልጉታል» ሲል መልሷል።

ዴፖሎ አርቴታና ዊሊያም ሳሊባ በሰሜን ለንደን መገኘታቸው ለተጨዋቹ ምቾት ሰጦታል፤ክለቡ ከፍተኛ ደረጃ ላይ ለሚገኘው ታዳጊ ወጣት ከስምምነት ላይ ለማድረስ ከፍተኛ ቦታ ተጫዋቹ እንዳሰጠው ተጠቁሟል።

«የትኛው ክለብ ተጨዋቹን ለማስፈረም ውድድሩን እየመራ እንደሆነ ለመናገር በጣም ገና ነው ብዬ አስባለሁ» ሲል አክሏል።
ነገር ግን ተጫዋቹ እንደ ሚኬል አርቴታ አይነት አሰልጣኝና አሰልጣኙ ስፓኒሽ የሚናገር በመሆኑና ዊሊያም ሳሊባ ከካሜሩን የመጣ በመሆኑ አርሰናል በፖል አመለካከት ቅድሚያ ተጨዋቹ እንደሰጠው ግምቱን አስቀምጧል።
«በእኔና በአርሰናል መካከል ግንኙነት አለ። ነገር ግን አሁን ትኩረታቸው ዝውውሩን ማሸነፍ ነው – ከዚያ በኋላ ሁሉም ነገር መስመር ይይዛል።»በማለት ወኪሉ ይገልጻል ።
እንደ ቢልድ የጀርመኑ ህትመት ዘገባ፣ መድፈኞቹ ኮፋኔን በቻምፒየንስ ሊግ የመጨረሻ 16 ድል ካሳዩበት ጊዜ ጀምሮ «ራዳቸው» እሱ ላይ እንደሆነ ይገልጻል፤ ከተጫዋቹ ወኪሎች ጋር አርሴናል «በቅርብ ግንኙነት» ላይ እንደሆነና ተጨዋቹን ሊያስፈርም ይችላል ሲል ገልጿል ።
ሆኖም፣ ኒውካስትል ኮፋኔን ለማዛወር ፉክክር ውስጥ ገብተዋል ። የሆፈንሃይም ክንፍ ተጫዋች ባዙማና ቱሬ ከፈረሙ በኋላ የካሜሩን ኢንተርናሽናል ተጫዋች ከስምምነት ለመድረስ ትኩረት አድርገው እየሰሩ ሊህን እንደሚችል ተነግሯል።
ማግፒስ በሚቀጥለው የውድድር ዘመን የቻምፒየንስ ሊግ እግር ኳስን ማረጋገጥ አለመቻላቸው ኮፋኔን የማግኘት ተስፋቸውን አሉታዊ ተጽዕኖ ሊያሳድር ይችላል፣ አርሰናል የፕሪሚየር ሊግ ተቀናቃኞቻቸውን በተጨዋቹ ድርድር እንደሚያሸንፉ እርግጠኞች ናቸው።

ሌቨርኩሰን ኮፋኔን ከአንድ አመት በኋላ ብቻ ለማጣት ፈቃደኛ ባይሆኑም፣ ሪፖርቱ የቡንደስሊጋውን ቡድን ወጣቱን እንዲሸጥ ለማድረግ 100 ሚሊዮን ዩሮ (86 ሚሊዮን ፓውንድ) የሚያወጣ ዋጋ በቂ ሊሆን እንደሚችል ይገልጻል።
«በሕይወቴ ውስጥ እንደ ኮፋኔ ብዙ ጥሪዎችን አጋጥመውኝ አያውቅም። አሁን በአውሮፓ ውስጥ ከ21 ዓመት በታች አጥቂና በጣም የተሟላ ችልታ ያለው ነው።»
«ፍጥነት፣ ቴክኒክ፣ በጣም ጥሩ መከላከልና በአየር ላይ የመጣ ኳስን በመምታት ጠንካራ ነው። እነዚህን ሁሉ ባህሪያት በአንድ አጥቂ ውስጥ ማግኘት በጣም ከባድ ነው።»
ከሌቨርኩሰን ከመባረራቸው በፊት የቀድሞው ዋና አሰልጣኝ ካስፐር ህጁልማንድ ኮፋኔን «ጥሩ የወደፊት ጊዜ እንዳለው» ነግረውታል።
«ለእኔ፣ ኮፊ በ2024 መጨረሻ ወደ አውሮፓ መጥቶ በ2025 የበጋ ወቅት ወደዚህ መዛወሩና ከዚያን ጊዜ ጀምሮ እንዴት እንዳደገ ስመለከት በጣም አስደናቂ ነው» ብለዋል።
