
ይህ የአሰልጣኞች ለውጥ የመጣው ግን በድንገት ሳይሆን አስቀድሞ በታቀደ ሁኔታ ነው። ዋና ዋናዎቹን ነጥቦችን እንደሚከተለው እንመልከት
የዴሻምፕ ስንብትና የዚዳን ሹመት

የታቀደ ስንብት፦ አሰልጣኝ ዲዲዬ ዴሻምፕ ከ2026 የዓለም ዋንጫ በኋላ ከፈረንሳይ ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝነነቱ በራሱ ፈቃድ እንደሚለቅ ገና በ2025 መጀመሪያ ላይ በይፋ አሳውቆ ነበር።
በስፔን ብሄራዊ ቡድን ትናትና ከተሸነፈ በኋላ የመልቀቁ ሁኔታ እውን ይሆናል ተብሎ ይጠበቃል፤ፈረንሳይ በ2026 የዓለም ዋንጫ የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታ በስፔን 2 ለ 0 በሆነ ውጤት መሸነፏ የዴሻምፕን የ14 ዓመታት ስኬታማ የሥልጣን ዘመን ማብቂያ አፋጥኖታል። ቡድኑ የፊታችን ቅዳሜ ለ3ኛ ደረጃ የሚደረገውን ጨዋታ ካደረገ በኋላ ዴሻምፕ በይፋ ከክለቡ ይለቃል ።
የዚዳን ስምምነት፦ የቀድሞው የሪያል ማድሪድ አሰልጣኝ ዚነዲን ዚዳን የፈረንሳይ እግር ኳስ ፌዴሬሽንን (FFF) ለመረከብ ገና በ2026 የፀደይ ወቅት ላይ የቃል ስምምነት አድርጎ ነበር። በአሁኑ ሰዓት ኮንትራቱን በይፋ ለመፈረም የመጨረሻዎቹ ዝርዝሮች (የረዳት ሰራተኞች ስብጥርን ጨምሮ) እየተጠናቀቁ እንደሚገኝ መረጃዎች እየወጡ ይገኛል።

የቀድሞ ኮከብ ተጫዋችና አሰልጣኝ ዚነዲን ዚዳን (Zinedine Zidane) የፈረንሳይ ብሔራዊ ቡድንን ሲረከብ በታክቲክና በስብስብ ደረጃ ትልቅ ለውጥ ያመጣል ተብሎ ይጠበቃል። እንደ ፈረንሳዩ ሌኪፕ (L’Équipe) ዘገባ ከሆነ፣ ዚዳን ቡድኑን እንዴት ማዋቀር እንዳለበትና ለትኞቹን ተጫዋቾች ቁልፍ ሚና መስጠት እንደሚገባው አስቀድሞ እቅድ አውጥቷል።
የሚጠበቁት ዋና ዋና የታክቲክ እና የስብስብ ለውጦች የሚከተሉት ይሆናሉ ተብሎ ይጠበቃል
1. የጨዋታ ፍልስፍናና የታክቲክ ለውጥ
የበለጠ ማጥቃትና ኳስን ተቆጣጥሮ መጫወት የዚዳን እቅድ ነው ፤ዲዲዬ ዴሻምፕ በተከላካይ ክፍሉ ጥንካሬና በጥንቃቄ ላይ ባተኮረ ታክቲክ የሚታወቅ ሲሆን፣ ዚዳን ግን በሪያል ማድሪድ ያሳየውን የመሃል ሜዳ የበላይነትን የመውሰድና የጨዋታውን ፍሰት የመቆጣጠር ስልት ይዞ ይመጣል ተብሎ ይጠበቃል።
ዚዳን የተጫዋቾች ነፃነት የሚሰጥ አሰልጣኝ ነው፤እንደ ክሊያን ምባፔ (Kylian Mbappé) ላሉ ኮከብ አጥቂዎች በሜዳ ላይ የበለጠ የመንቀሳቀስ ነጻነት በመስጠት የማጥቃት አቅማቸውን በከፍተኛ ደረጃ ለመጠቀም ይሞክራል ተብሎ ይጠበቃል።

2. የስብስብና የተጫዋቾች ለውጥ
የምባፔና የዚዳን ጥምረት፦ምባፔ ከልጅነት አምልኮቱ ዚዳን ጋር አብሮ ለመስራት ከፍተኛ ፍላጎት ያለው ሲሆን፣ ዚዳንም ምባፔን የቡድኑ ፍጹም መሪ በማድረግ በእሱ ላይ ቡድኑን እንደሚገነባው ይገመታል።
ዚዳን ለአዳዲስ ወጣቶች ዕድል ይሰጣል እንደ ማይክል ኦሊሴ (Michael Olise)፣ ብራድሌይ ባርኮላ (Bradley Barcola) እና ራያን ቼርኪ ያሉ ወጣት ተሰጥኦዎች በዚዳን ስር የበለጠ የመሰለፍ ዕድል ያገኛሉ ተብሎ ይታመናል።
የመሃል ሜዳ ለውጥ በተመለከተ በዴሻምፕ የመጨረሻ ዘመን የተወሰነ ቦታ አጥተው የነበሩት እንደ ኤድዋርዶ ካማቪንጋ (Eduardo Camavinga) ያሉ የመሃል ሜዳ ተጫዋቾች በዚዳን ስር ትልቅ ሚና ሊሰጣቸው ይችላል ይሚል ግምት አለ።
3. የረዳት ሰራተኞችና የቴክኒክ ቡድን ለውጥ
ዚዳን የቀድሞ አብረውት የሰሩትን አሰልጣኞች የመጥራት እቅድ አለው ዚዳን ሰፊ የስራ አጋሮችን ይዞ ለመምጣት ፌዴሬሽኑን የጠየቀ ሲሆን፣ በሪያል ማድሪድ ስኬታማ ጊዜያት አብሮት የነበረው የእሱ ቀኝ እጁ ዳቪድ ቤትቶኒ (David Bettoni) ረዳት አሰልጣኝ አድርጎ እንደሚሾም ይጠበቃል።
የዳታና የአናሊቲክስ ክፍል በተመለከተ ቡድኑን በዘመናዊ የዳታ ትንተና (Data Analytics) ለማገዝ አዲስ የባለሙያዎች ቡድን ለማዋቀር አቅዷል።
ዚዳን የመጀመሪያ ጨዋታዎቹን በሴፕቴምበር ወር በሚጀምረው የኔሽንስ ሊግ (Nations League) ውድድር ላይ ከጣሊያን፣ ከቤልጂየምና ከቱርክ ብሄራዊ ቡድን ጋር እንደሚያደርግ ይጠበቃል።
