
ሊዮኔል መሲ በትላንትናው ጨዋታ ያሳየው ብቃት በ39 ዓመቱ የማይታመንና እድሜ ቁጥር ብቻ መሆኑን በድጋሚ ያረጋገጠበት ነበር ። በ88% ኳስ ይዛ ወደ ኋላ ባፈገፈገችው የእንግሊዝ ብሔራዊ ቡድን ላይ ጨዋታውን ሙሉ በሙሉ የተቆጣጠረው መሲ፣ አርጀንቲናን 2 ለ 1 አሸንፋ ወደ ዓለም ዋንጫው ፍጻሜ እንድትሸጋገር ዋናውን ሚና ተጫውቷል።
ከትላንትናው ጨዋታ በኋላ የሚዲያ ተንታኞችና ደጋፊዎች መሲን ከዲዬጎ ማራዶና ጋር እያመሳሰሉት ይገኛሉ የመጡባቸው ዋና ዋና አንደኛው ምክንያት የመሪነት ስነ-ልቦና (The Diego Aura) አንዱ ነው።

ማራዶና በ1986 የዓለም ዋንጫ ላይ ቡድኑን ብቻውን ተሸክሞ ለስኬት እንዳበቃው ሁሉ፣ መሲም በትላንትናው ጨዋታ የአርጀንቲናን ወጣቶች መርቶና ሜዳ ላይ ፍጹም መረጋጋትን ሰጥቶ ሲጫወት ታይቷል ።በእለቱ አርጀንቲና ላገባቻቸው ግቦች ፈጣሪ ነበር ።
እንግሊዝ የተከላካይ ቁጥር አብዝታ በዘጋችበት አስቸጋሪ ሰዓት፣ መሲ በጠበበ ክፍተት ውስጥ ድንቅ የሆኑ ሁለት ኳሶችን (assists) አመቻችቶ በማዘጋጀት የመከላከል ግንቡን ሰብሯል። ይህ አስማታዊ እይታው (vision) ማራዶና ቤልጂየም እና እንግሊዝ ላይ ካሳየው ታሪካዊ ክህሎቶች ጋር እንዲመሳሰል አድርጎታል።

ሌላው ምክንያት ማራዶና በአርጀንቲና እግር ኳስ ታሪክ ውስጥ የማይደገም ተብሎ ይታሰብ ነበር፤ ነገር ግን መሲ በዚህ 39 አመቱ እድሜው ቡድኑን ለሁለተኛ ጊዜ ወደ ዓለም ዋንጫ ፍጻሜ መምራቱ ከማራዶና እኩል አልፎ ተርፎም የበለጠ ታላቅ ያደርገዋል የሚል ነጥብ አሰጥቶታል ።
በአጠቃላይ ትላንትና የታየው የሜሲ ብቃት የክላሲክ «ቁጥር 10» ሚና ምን መምሰል እንዳለበት ለአለም ያሳየና ማራዶናዊ መንፈስ የታየበት ነበር።
ነገር ግን በትላንትናው ጨዋታ ዙሪያ በዓለም አቀፍ የእግር ኳስ ተንታኞችና ደጋፊዎች መካከል የተፈጠረውን ትልቅ ክርክር በሁለት እይታዎች ማየት ይቻላል፦

1ኛ. ከማራዶና ጋር መምሰሉ ፍጹም ትክክል ነው የሚለው እይታ
ብቸኛ መሪነት (One-Man Show)፦ ማራዶና በ1986 የዓለም ዋንጫ አርጀንቲናን ብቻውን ተሸክሞ ዋንጫ እንዳነሳው ሁሉ፣ መሲም በትላንትናው ጨዋታ በ39 ዓመቱ ወጣቱን ስብስብ መርቶና በታክቲክ የተዘጋውን የእንግሊዝን መከላከል በሁለት አስማታዊ ኳሶች (Assists) ሰብሮ በማቀበል ቡድኑን ወደ ፍጻሜ አምጥቷል።
መሲ በአሁኑ ሰዓት ለአርጀንቲና ሕዝብ ያለው ቦታ እና ሜዳ ላይ የሚያሳየው ስሜታዊ መሪነት ቀደም ሲል ማራዶና ከነበረው «መለኮታዊ»ከሚባል ተሰሚነት (Aura) ጋር ፍጹም ተመራጭ ያደርገዋል።
2ኛ. ሁለቱን ማወዳደር ስህተት ነው የሚለው እይታ
ማራዶና የተጫወተበት ዘመን ተከላካዮች በጣም ደካማና ሕጉ የማይጠብቀው፣ ሜዳዎችም አስቸጋሪ የነበሩበት ወቅት ነው። መሲ ደግሞ ዘመናዊና የተጫዋቾች ጥበቃ ባለበት እግር ኳስ ላይ ነው እየተጫወተ ነው ያለው።

የጨዋታ ስልት ልዩነት፦ ማራዶና በኳስ ቁጥጥር እና ተከላካዮችን በመቀነስ (Dribbling) የሚታወቅ እግር ኳስ ተጫዋች ሲሆን፤ ሜሲ በአሁኑ እድሜው (39 ዓመቱ) በሜዳ ላይ ብዙ ሳይሮጥ፣ በአእምሮ ብስለትና በቦታ አጠቃቀም (Spatial awareness) ብቻ ጨዋታውን የሚቀይር ስልጡን ተጫዋች ነው።
በአጠቃላይ፣ ሁለቱም በአርጀንቲና ታሪክ ውስጥ የማይደገሙ ታላላቅ «የቁጥር 10» ምልክቶች በመሆናቸው በትላንትናው ጨዋታ መሲ ያሳየው ድንቅ ብቃት ማራዶናን እንዲያስታውሱን ማድረጉ ተፈጥሯዊ ነው።

የእግር ኳስ ተንታኞችና ደጋፊዎች ማራዶናን እና መሲን የሚያወዳድሩባቸውን ዋና ዋና ምክንያቶች እንመልከት፡
ዲዬጎ ማራዶናን ቀዳሚ የሚያደርጉት ምክንያቶች፡
–የመሪነት ተፅዕኖ እና ስሜት (Aura)፦ ማራዶና በ1986 የዓለም ዋንጫ ላይ ያሳየው ብቃት ቡድኑን ብቻውን ተሸክሞ ለዋንጫ ያበቃበትና መላው የአርጀንቲና ሕዝብ እንደ መለኮታዊ ኃይል የሚያየው ታሪካዊ መሪ ነበር።
የማራዶና የተጫወተበት ዘመን ተከላካዮች በጣም ደካማ የነበሩበት፣ ዳኞች ለፈጣሪ ተጫዋቾች ጥበቃ የማያደርጉበትና ሜዳዎቹም አስቸጋሪ የነበሩበት በመሆኑ ያሳየው ጥበብ የበለጠ ተአምራዊ ተደርጎ ይወሰዳል።
ሊዮኔል ሜሲን ቀዳሚ የሚያደርጉት ምክንያቶች፡
–የረጅም ጊዜ ወጥነት (Consistency)፦ ማራዶና በከፍተኛ ብቃት ላይ የቆየው ለጥቂት ዓመታት ብቻ ሲሆን፣ መሲ ግን ለ20 ዓመታት ያህል በአለም እግር ኳስ አናት ላይ ያለ ማቋረጥ መቆየት ችሏል።
አሁንም በ39 ዓመቱ እያሳየው ያለው ድንቅ ብቃት፦ በትላንትናው ጨዋታ እንዳየነው፣ በ39 ዓመቱ ቡድኑን ለሁለተኛ ጊዜ ወደ ዓለም ዋንጫ ፍጻሜ መምራቱና በዘመናዊው እግር ኳስ ያስመዘገባቸው ስፍር ቁጥር የሌላቸው ግቦችና ክብረ ወሰኖች ከማራዶና በላይ ታላቅ ያደርገዋል የሚያሰኙት ናቸው።
