
ዚነዲን ዚዳን የፈረንሳይ ብሔራዊ ቡድንን (Les Bleus) አዲስ ዋና አሰልጣኝ ለመሆን ሙሉ የቃል ስምምነት ላይ ደርሷል። ታዋቂው ጋዜጠኛ ፋብሪዚዮ ሮማኖ እንደዘገበው ዚዳን የአሰልጣኝነት ስታፎቹን በሙሉ አደራጅቶ ጨርሷል።
የወቅቱ አሰልጣኝ ዲዲዬ ዴሻምፕ ትናት ማታ ፈረንሳይ ከእንግሊዝ ጋር ለዓለም ዋንጫ 3ኛ ደረጃ የተደርገውን ጨዋታ ከመራ በኋላ በይፋ ከኃላፊነቱ ተነስቷል።
ዚዳን ለፈረንሳይ ብሔራዊ ቡድን የ4 ዓመት ውል የሚፈርም ሲሆን፥ ዋናው ግቡ ቡድኑን ለዩሮ 2028 እና ለ2030 ዓለም ዋንጫ ማዘጋጀት ነው።

ዚነዲን ዚዳን የፈረንሳይ ብሔራዊ ቡድንን በይፋ ለመረከብ ከፈረንሳይ እግር ኳስ ፌዴሬሽን (FFF) ጋር ሙሉ ስምምነት ላይ ደርሷል።
ዚዳን በዓመት 7.5 ሚሊዮን ዩሮ (በአጠቃላይ ለ 4 ዓመት 30 ሚሊዮን ዩሮ) ለማግኘት ተስማምቷል። የፈረንሳይ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ለብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ የጣለውን የ€450,000 ዓመታዊ የደመወዝ ጣሪያ (Salary Cap) በመጣስ ለዚዳን ከፍተኛውን ክፍያ ለመፈጸም ከስፖርት ሚኒስቴር ልዩ ፈቃድ (Exemption) ለማውጣት እየሰራ ይገኛል።
የውል ሰነዶች ማጠናቀቂያ እስከ ሐምሌ 14 (ጁላይ 21) የሚቆይ ሲሆን፥ ይፋዊው የአሰልጣኝነት ማስታወቂያ ከሐምሌ 16 እስከ 17 (ጁላይ 23-24) ባሉት ቀናት ውስጥ ለሕዝብ ይፋ ይደረጋል።
ዚዳን በይፋ ሥራውን በጳጉሜ ወር (ሴፕቴምበር 2026) የሚጀምር ሲሆን፥ የመጀመሪያ ፈተናዎቹ በኔሽንስ ሊግ ከጣሊያን፣ ቤልጂየምና ከቱርክ ጋር የሚደረጉ ጨዋታዎች ይሆናሉ።
ዚዳን በአሰልጣኞችና በቴክኒክ ስታፉ ውስጥ (በጠቅላላው 25 አባላት ይኖሩታል) የሴቶችን ተሳትፎና ውክልና በከፍተኛ ደረጃ ለማሳደግም ልዩ ዕቅድ መያዙ ታውቋል።

የፈረንሳይ ብሔራዊ ቡድንን ለመረከብ የተስማማው ዚነዲን ዚዳን፣ ቡድኑን ወደ ቀድሞ ክብሩ ለመመለስና አዲስ የውድድር ዘመን ለመጀመር የረጅም ጊዜ ስትራቴጂያዊ ዕቅዶችን አውጥቷል።
የዚዳን ዋና ዋና አዲስ ዕቅዶች የሚከተሉት ናቸው፦
- የኪሊያን ምባፔን አቅም በከፍተኛ ደረጃ መጠቀም
ዚዳን በሪያል ማድሪድ ቤት በነበረው ልምድና ከምባፔ ጋር ባለው ጥልቅ ግላዊ ግንኙነት በመጠቀም፣ ተጫዋቹን የቡድኑ ፍጹም መሪና ቁልፍ ሰው የማድረግ ዕቅድ አለው።
ባለፉት ውድድሮች በዲዲዬ ዴሻምፕ ታክቲክ ውስጥ ሲቸገር የነበረውን ምባፔን፣ ሙሉ ነፃነት በመስጠት የማጥቃት ብቃቱን በከፍተኛ ደረጃ ለማሳደግ አልሟል።
- የአማካይ መስመሩን በሪያል ማድሪድ ኮከቦች ዙሪያ መገንባት
ዚዳን አዲሱን የፈረንሳይ አማካይ መስመር ሙሉ በሙሉ በወጣቶቹ የሪያል ማድሪድ ኮከቦች ኦሬሊየን ቹአሜኒ (Aurelien Tchouameni) እና ኤድዋርዶ ካማቪንጋ (Eduardo Camavinga) ዙሪያ ለመገንባት አቅዷል።
እነዚህን ተጫዋቾች በቅርበት ስለሚያውቃቸው፣ የቡድኑን የመሃል ክፍል ፍጥነትና ጉልበት ለመጨመር ዋነኛ የፊት መስመር ተመራጮቹ ያደርጋቸዋል።
- ለአዳዲስ ወጣት ተሰጥኦዎች ዕድል መስጠት
ዴሻምፕ ያዘወትራቸው በነበሩት አንጋፋ ተጫዋቾች ላይ ብቻ ከማተኮር ይልቅ፣ በአውሮፓ ሊጎች አስደናቂ ብቃት እያሳዩ ያሉ አዳዲስ ወጣት ፈረንሳውያን ተጫዋቾችን ወደ ብሔራዊ ቡድኑ በማምጣት ስብስቡን የማጠናከር ዕቅድ አለው።
ቡድኑን ይበልጥ ፈጣን፣ ቀጥተኛ ጥቃት የሚሰነዝር እና ማራኪ እግር ኳስ የሚጫወት ለማድረግ ታክቲኩን ይቀይራል ተብሎ ይጠበቃል።
- የዩሮ 2028 እና የ2030 ዓለም ዋንጫ ግቦች
የዚዳን ዋነኛ እና ትልቁ ዕቅድ ፈረንሳይን ለቀጣዩ የአውሮፓ ዋንጫ (Euro 2028) ማዘጋጀትና ውድድሩን በድል ማጠናቀቅ ነው።
የተሰጠውን የ4 ዓመት ውል በመጠቀም ቡድኑ ለ2030 ዓለም ዋንጫ ጠንካራ ተፎካካሪ ሆኖ እንዲቀርብ የመሠረት ድንጋይ ማስቀመጥ ከወዲሁ ይኖርበታል።
ዚነዲን ዚዳን የፈረንሳይ ብሔራዊ ቡድንን ሲረከብ በተለመደው የአሰልጣኞች ቁጥር ሳይወሰን በሰፊና በዘመናዊ መዋቅር ለመደራጀት አቅዷል።
ታማኙ ረዳት ዴቪድ ቤትቶኒ (David Bettoni)፦ በሪያል ማድሪድ ስኬታማ የነበረውና የዚዳን ቀኝ እጅ የሆነው ቤትቶኒ የመጀመሪያው ረዳት አሰልጣኝ ሆኖ የጋይ ስቴፋንን ቦታ ይረከባል ።
ዚዳን ከፈረንሳይ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ጋር ባደረገው ስምምነት መሠረት፣ የተቃዋሚዎችን እና የተጫዋቾችን ብቃት በቴክኖሎጂ የሚተነትን ልዩ የዳታ እና አናሊቲክስ ቡድን በስታፉ ውስጥ ያዋቅራል።
ተጫዋቾች በትልልቅ ውድድሮች ላይ የሚገጥማቸውን ጫና ለመቋቋም እንዲችሉ የስነ-ልቦና ባለሙያዎችን በቋሚነት በቡድኑ ዙሪያ ለማስቀመጥ አቅዷል።
