ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በተለያዩ የእግር ኳስ ውድድሮች ላይ በጨዋታ አመራሮች ላይ የሚፈጸሙ አካላዊ ጥቃቶችን የሚያሳዩ ምስሎች በተለያዩ የማህበራዊ መገናኛ ዘዴዎች በስፋት ሲሰራጩ እየተመለከትን እንገኛለን። እነዚህ አሳዛኝ ድርጊቶች በወቅቱ፣ በጥብቅ እና በተቀናጀ መልኩ መቆጣጠር ካልተቻለ በእግር ኳሳችን ላይ የሚያስከትሉት ጉዳት ከፍተኛ ነው።

የጨዋታ አመራሮች የእግር ኳስ ውድድሮች በሕግ፣ በፍትሃዊነት እና በስፖርታዊ ሥነ-ምግባር እንዲመሩ ወሳኝ ሚና የሚጫወቱ ባለሙያዎች ናቸው። በመሆኑም ደህንነታቸው አስተማማኝ ባልሆነ ሁኔታ ውስጥ ወደ ውድድር እንዳይመደቡ በቂ ጥንቃቄ ማድረግ፣ ለእግር ኳስ ቤተሰቡ ሰፊ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎችን ማከናወን እና በእነርሱ ላይ የሚፈጸሙ ጥቃቶችን በሕግ አግባብ ተጠያቂነትን ማረጋገጥ ወሳኝ ነው።

ይህንን ችግር በጋራ ኃላፊነት እና በተቀናጀ አሰራር ማስቆም ካልቻልን፣ ለወደፊት ተስፋ የሚሆኑ ወጣት የጨዋታ አመራሮችን ለማፍራት የምናደርገውን ጥረት ከፍተኛ ፈተና ውስጥ ይከተዋል።

የጨዋታ አመራሮች የእግር ኳስ ልማት ዋና አካል ናቸው። የእነርሱን ክብር፣ ደህንነት እና መብት መጠበቅ የዛሬን እና የነገን እግር ኳስ መጠበቅ ማለት ነው።

በመሆኑም በየደረጃው የምትገኙ የእግር ኳስ ፌዴሬሽን አመራሮች፣ የዳኞች ኮሚቴዎች እና ሁሉም የእግር ኳስ ቤተሰብ ይህንን ጉዳይ በከፍተኛ አፅንኦት በመያዝ፣ የጨዋታ አመራሮችን ለመጠበቅ የየራሳችንን ኃላፊነት በመወጣት የእግር ኳስ ዳኝነት ሙያን እና የስፖርቱን ዕድገት በጋራ እንድናሳድግ ጥሪ እናቀርባለን።

ለዘላቂ የእግር ኳስ ልማት፣ የጨዋታ አመራሮችን ክብርና ደህንነት በጋራ እንጠብቅ በማለት ኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ብሔራዊ የዳኞች ኮሚቴ አሳውቋል

Facebooktwitterlinkedinyoutubetumblrinstagramflickrfoursquaremail
Facebooktwitterredditpinterestlinkedintumblrmail

By admin

Hello, dear. I am Wosenseged Mersha Demissie. Author, Journalist, and Sociological Criticism. He has worked in several media in Ethiopia and foreign media also. I have come to my country, Ethiopia, from abroad, and for the past eight years, I have been giving political analysis and writing in magazines, newspapers, and televisions on all the free press in Ethiopia. I have six books that I wrote and published during my stay abroad and after I came back to my country and are on the market. Above all, I feel spiritual satisfaction for coming from a developed country and working in a country where there is no freedom of the press. I have sacrificed a lot in this profession. Imprisonment, abuse—I was crushed economically. I have been living separately from my family for many years, but I am happy and proud of my career to be a voice for the voiceless people of Ethiopia, whom I love and respect by working in the press without payment. After leaving my country and returning to my country, Growing up in Arat Kilo, YMCA, I was exposed to various sports. I know many sports. I have worked as a referee, player, and tournament organizer. As a result, I have worked as a sports editor on radio, television, and newspapers for many years. I have worked alongside other media outlets for more than 20 years by preparing and publishing my own sports newspaper called San George.I have traveled to many countries, including Europe, the Far East, Asia, Oceania, and Africa, and have been present at many competitions, including athletics.This is because I have this love for sports. I have reopened this media outlet for sports. In addition to this, I have worked for the past 30 years. May God protect Ethiopia and its people and give peace and love to our world. Thank you anyway. Wosenseged Mersha Demissie Author, Journalist, Sociological Criticism

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *