
ብሩኖ ጊማሬሽ (Bruno Guimarães) ወደ አርሰናል የሚያደርገው ዝውውር የመጨረሻ ምዕራፍ ላይ ደርሷል። አብዛኞቹ ታማኝ ዓለም አቀፍ የስፖርት መገናኛ ብዙኃን ዝውውሩ በዚህ ቅዳሜና እሁድ ሙሉ በሙሉ እንደሚጠናቀቅ እየዘገቡ ይገኛሉ።
የስምምነቱ ዝርዝር ሁኔታ
አርሰናል ለኒውካስል ዩናይትድ 70 ሚሊዮን ፓውንድ ቋሚ ክፍያ (ከ90 ሚሊዮን ዩሮ በላይ) እና በተጨማሪ 10 ሚሊዮን ፓውንድ ማበረታቻ (Performance-related bonuses) በድምሩ 80 ሚሊዮን ፓውንድ ለመክፈል ሙሉ ስምምነት ላይ ደርሷል።
የ28 ዓመቱ ብራዚላዊ አማካኝ ከአርሰናል ጋር እስከ ሰኔ 2031 ዓ.ም (ለአምስት ዓመታት) የሚቆይ ውል ለመፈረም የግል ጥቅማጥቅሞችን ሙሉ በሙሉ ተስማምቷል።
ጊማሬሽ በኒውካስል የቅድመ-ውድድር ዝግጅት ስብስብ ውስጥ ያልተካተተ ሲሆን፣ በዚህ ሳምንት መጨረሻ ለሕክምና ምርመራ እና ፊርማውን ለማኖር ወደ ለንደን እንደሚያቀና ESPN ዘግቧል።

ከኒውካስል በኩል ያለው መረጃ
ኒውካስል አካባቢ የሚወጡ አንዳንድ የአገር ውስጥ ጋዜጠኞች (እንደ ሊ ራይደር ያሉ) ክለቡ አዲስ ለሚሾመው አሰልጣኝ ማትያስ ጃይስሌ (Matthias Jaissle) ዕድል ለመስጠት ዝውውሩ ገና በይፋ አልተቋጨም ቢሉም፣ የዴቪድ ኦርንስታይን (The Athletic) እና የቢቢሲ (BBC Sport) መረጃዎች ግን ዝውውሩ ወደኋላ እንደማይመለስና መጠናቀቁ አይቀሬ መሆኑን እያረጋገጡ ነው።
ቡሩኖ ጊማሬሽ ዛሬ የሕክምና ምርመራውን ያደርጋል ተብሎ የነበረ ቢሆንም ሕክምናውን ግን አላደረገም፤ ነገር ግን የመጨረሻ ስምምነት ላይ ስለተደረሰ የሕክምና ምርመራው በሚቀጥለው ሰኞ (ነሐሴ 3 ቀን 2026 እ.አ.አ) እንዲያደርግ ቀጠሮ ተይዞለታል።
ስለ ዝውውሩ የመጨረሻ ምዕራፍ የወጡት ትኩስ ዝርዝር መረጃዎች የሚከተሉት ናቸው፦
አርሰናል በለንደን ኮልኒ (London Colney) የሥልጠና ማዕከሉ ለተጫዋቹ የሕክምና ምርመራ ለማድረግ የሰኞውን ዕለት በይፋ ቀጠሮ ይዟል።
እንደ የቫን ቃሳግራንዴ (Venê Casagrande) መረጃ አርሰናል ለኒውካስል ዩናይትድ 75 ሚሊዮን ፓውንድ ቋሚ ክፍያ ለመክፈል የተስማማ ሲሆን፣ ከሌሎች ማበረታቻዎች ጋር በአጠቃላይ ሂሳቡ 80 ሚሊዮን ፓውንድ ይደርሳል።
ተጫዋቹ መጀመሪያ ከተባለው አምስት ዓመት ይልቅ እስከ ሰኔ 2030 ዓ.ም ድረስ (ለ4 ዓመታት) በለንደን ለመቆየት በግል ጥቅማጥቅሞች ላይ ሙሉ ስምምነት ላይ ደርሷል።
