የኢትዮጵያ ቦክስ ፌዴሬሽን 20ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤውን በሀርሞኒ ሆቴል አካሂዷል።

መደበኛ ጉባኤው አቶ እያሱ ወሰንን የኢትዮጵያ ቦክስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት አድርጎ መርጧል።

የኢትዮጵያ ቦክስ ፌዴሬሽን ባካሄደው መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ ያለፈውን ጉባኤ ቃለ ጉባኤ በማፅደቅ በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ መክሯል።

መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤው በበጀት ዓመቱ እቅድ አፈፃፀም፣ በተሻሻለው የፋይናንስ መመሪያ፣ እንዲሁም የፕሬዚዳንትና የሥራ አስፈፃሚ ምርጫ በአጀንዳነት ይዞ ከመከረባቸው አጀንዳዎች መካከል ይገኙበታል።

ፌዴሬሽኑ በባለፉት ዓመታት ዓለምአቀፍ ውድድሮች በሀገር ውስጥ እንዲካሄዱ ማድረጉ እና የተሻለ ዓለምአቀፍ ግንኙነቶች መፍጠር መቻሉ በጥንካሬ ጉባኤው ያነሳቸው ጉዳዮች ናቸው።

በሌላ መልኩ ፌዴሬሽኑ የቦክስ ቁሳቁሶች ድጋፍ ጨምሮ ስልጠናዎችን መስጠት መቻሉ በስኬት ተነስተዋል።

የዳኞች የውሳኔ አሰጣጥ አሰራር ሥርዓት መስተካከል እንዳለበት ጉባኤው አፅዕኖት የሰጠበት ጉዳይ ሲሆን የአሰልጣኝነት የፈቃድ አሰጣጥ መስተካከል እንዳለበትም ጉባኤው ተወያይቶበታል።

የቦክስ ስፖርትን በተሻለ መንገድ ለማስቀጠል ከክልልና ከተማ አስተዳደር ጋር ቅንጅታዊ ሥራዎች መኖር እንዳለበት ያመላከተው ጉባኤው ክለቦችን ማስፋፋት ትኩረት እንዲሰጥም መደበኛ ጉባኤው አቅጣጫ ሰጥቶበታል።

የኢትዮጵያ ቦክስ ፌዴሬሽን የሚያካሄዳቸው ዓመታዊ ውድድሮችና ስልጠናዎች በክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች እውቅና ሊኖራቸው እንደሚገባ በጉባኤው ተመላክቷል።

የፌዴሬሽኑ ፕሬዚዳንት ሆነው በ9 ድምፅ ዳግም የተመረጡት አቶ እያሱ ወሰን በጉባኤው ማጠቃላያ ባስተላለፉት መልዕክት አዲሱ አመራር የስፖርቱን ደረጃ ለማሳደግ በቁርጠኝነት ይሰራል ብለዋል።

ብቃት ያላቸውን አትሌቶች ለማፍራት እና ፌዴሬሽኑን በፋይናንስ ራሱን ወደ መቻል ለማሸጋገር ያለመ ሰፊ እቅድ ይዞ እንደሚስራም ገልፀዋል።

​ በተለይም በኦሊምፒክ እና በዓለምአቀፍ መድረኮች የሀገራችንን ሰንደቅዓላማ ከፍ አድርገው የሚያውለበልቡ አትሌቶችን ለማፍራት ከስፖርቱ ባለድርሻ አካላት ጋር በጋራ እንደሚሰሩ አቶ እያሱ አስታውቀዋል።

ከዚህ ቀደም ከክልሎች ጋር የነበረውን ግንኙነት የበለጠ በማጠናከር ተገቢውን ድጋፍ በመስጠትና የእለት ተእለት የጋራ ግብ በመቅረጽ የቦክስ ስፖርት በመላው ሀገሪቱ እንዲስፋፋ ይደረጋልም ብለዋል ፕሬዚዳንቱ።

አትሌቶች ሁልጊዜም በከፍተኛ ዝግጅት እና ብቃት ውስጥ እንዲቆዩ ለማድረግ በየሳምንቱ እና በየጊዜው በመላ ሀገሪቱ ውድድሮች እንደሚካሄዱ አመላክተዋል።

የጋራ ጥረትን በመጠቀም ቦክስ ሀገራችን የምትኮራበት ስፖርት እንዲሆን ጠንክረው እንደሚሰሩም አረጋግጠዋል።

የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ተወካይ አቶ ከበደ እጅጉ በበኩላቸው በስፖርት ማህበራት ህግ መሠረት የስፖርት ማህበራት በወቅቱ ጉባኤያቸውን ማካሄድ እንዳለባቸው አስገንዝበዋል።

የስፖርት ማህበራት በተሰጣቸው እውቅና መሠረት የስፖርት ማህበራት የፋይናንስ አቅማቸውን በማጠናከር ሀገራቸውን በዓለምአቀፍ ደረጃ የሚያስጠሩና የሚወክሉ ስፖርተኞችን ማፍራት ቀዳሚ ስራቸው እንዲሆን አቅጣጫ ሰጥተዋል።

የኢትዮጵያ ቦክስ ፌዴሬሽን ባካሄደው 20ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ ከፕሬዚዳንቱ በተጨማሪ ሥድስት ሥራ አስፈፃሚ በመምረጥ ተጠናቋል።

Facebooktwitterlinkedinyoutubetumblrinstagramflickrfoursquaremail
Facebooktwitterredditpinterestlinkedintumblrmail

By admin

Hello, dear. I am Wosenseged Mersha Demissie. Author, Journalist, and Sociological Criticism. He has worked in several media in Ethiopia and foreign media also. I have come to my country, Ethiopia, from abroad, and for the past eight years, I have been giving political analysis and writing in magazines, newspapers, and televisions on all the free press in Ethiopia. I have six books that I wrote and published during my stay abroad and after I came back to my country and are on the market. Above all, I feel spiritual satisfaction for coming from a developed country and working in a country where there is no freedom of the press. I have sacrificed a lot in this profession. Imprisonment, abuse—I was crushed economically. I have been living separately from my family for many years, but I am happy and proud of my career to be a voice for the voiceless people of Ethiopia, whom I love and respect by working in the press without payment. After leaving my country and returning to my country, Growing up in Arat Kilo, YMCA, I was exposed to various sports. I know many sports. I have worked as a referee, player, and tournament organizer. As a result, I have worked as a sports editor on radio, television, and newspapers for many years. I have worked alongside other media outlets for more than 20 years by preparing and publishing my own sports newspaper called San George.I have traveled to many countries, including Europe, the Far East, Asia, Oceania, and Africa, and have been present at many competitions, including athletics.This is because I have this love for sports. I have reopened this media outlet for sports. In addition to this, I have worked for the past 30 years. May God protect Ethiopia and its people and give peace and love to our world. Thank you anyway. Wosenseged Mersha Demissie Author, Journalist, Sociological Criticism

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *