ኢትዮጵያኖች የራሳችሁን ሰዓት ከማሻሻል ውጭ አልቀናቸውም

የለንደን ዳይመንድ ሊግ (London Diamond League) ትላንት በተካሄደው ውድድር ጆሽ ኬር (Josh Kerr) የዓለም ክብረ ወሰንን የሰበረበት ድንቅ ምሽት ነበር። ኬር የ 1 ማይል ርቀትን በ 3:42.66 በመጨረስ የአልጄሪያዊውን ሂሻም ኤል ጉሩጅን የቆየ ክብረ ወሰን ማሻሻል ችሏል።
ሌሎች የትላንቱ አበይት ውጤቶች፦

የሴቶች 800 ሜትር፦ ኪሊ ሆጅኪንሰን (Keely Hodgkinson) በ 1:56.21 አንደኛ በመሆን አሸንፋለች።

የሴቶች 200 ሜትር፦ ጁሊየን አልፍሬድ (Julien Alfred) በ 21.66 በማጠናቀቅ አሸናፊ ሆናለች።

የወንዶች 100 ሜትር፦ ካይንሶላ አጃዪ (Kayinsola Ajayi) በ 9.84 ሰከንድ አሸንፏል።

የወንዶች 400 ሜትር፦ ሬይ ቤንጃሚን (Rai Benjamin) አንደኛ ሲወጣ፣ ማቲው ሃድሰን-ስሚዝ ሁለተኛ ሆኗል።

የኢትዮጵያ አትሌቶች ከፍተኛ ፉክክር ያስመዘገቡ ሲሆን፣ ፅጌ ዱጉማ በ 800 ሜትር 3ኛ ደረጃን በመያዝ ብቸኛውን የመድረክ (ፖዲየም) ውጤት ማስመዝገብ ችላለች። በተጨማሪም በሴቶች 3,000 ሜትር በርካታ አትሌቶች የግል እና የዓመቱን ምርጥ ሰዓቶቻቸውን አሻሽለዋል።

ለንደን ዳይመንድ ሊግ አትሌት ፋንታዬ በላይነህ የግል ምርጥ ሰዓቷን በማሻሻል 5ኛ ሆና አጠናቀቀች፤ ፅጌ ዱጉማ በ800 ሜትር 3ኛ ደረጃን ያዘች ።

የ2026 የዋንዳ ዳይመንድ ሊግ 11ኛ መዳረሻ ውድድር በለንደን በከፍተኛ ፉክክር ተካሂዶ ሲጠናቀቅ፣ በሴቶች 3,000 ሜትር አውስትራሊያዊቷ ጀሲካ ሀል 8:24.69 በመሮጥ ድል ቀንታለች።

ኢትዮጵያዊቷ ፋንታዬ በላይነህ ደግሞ የግል ምርጥ ሰዓቷን 8:26.98 በማሻሻል 5ኛ ደረጃን ይዛ አጠናቃለች።

በውድድሩ ኢትዮጵያውያን ወጣት አትሌቶችም የግል ምርጥ እና የዓመቱ ምርጥ ሰዓቶቻቸውን በማሻሻል ተስፋ ሰጪ ብቃት አሳይተዋል።

ፋንታዬ በላይነህ የግል ምርጥ ሰዓቷን በማሻሻል የአለም ደረጃ ውድድር ላይ ተወዳዳሪነቷን እያጠናከረች መሆኗን አሳይታለች።

በተመሳሳይ መዲና ኢሳ እና ሒሩት መሸሻ የዓመቱን ምርጥ ሰዓት ሲያስመዘግቡ፣ ማርታ አለማየሁም የግል ምርጥ ሰዓቷን አሻሽላለች።

የኢትዮጵያ አትሌቶች ውጤት – 3,000 ሜትር

5ኛ – ፋንታዬ በላይነህ – 8:26.98 (PB)
8ኛ – መዲና ኢሳ – 8:27.99 (SB)
9ኛ – ሀዊ አበራ – 8:28.00
10ኛ – ማርታ አለማየሁ – 8:29.09 (PB)
12ኛ – ሒሩት መሸሻ – 8:32.04 (SB)

የሴቶች 800 ሜትር ፉክክር፣ ከኢትዮጵያ ብቸኛ ተወዳዳሪ የነበረችው ፅጌ ዱጉማ 1:56.92 በመሮጥ 3ኛ ደረጃን በመያዝ መድረኩን አጠናቀቀች።


ይህም የ2026 የውድድር አመቷ ምርጥ ውጤት ነው።
ፅጌ ዱጉማ በጠንካራ የመጨረሻ 200 ሜትር ሩጫ 3ኛ ደረጃዋን በማረጋገጥ ለኢትዮጵያ ብቸኛውን የመድረክ ውጤት አስመዝግባለች።

የለንደን ዳይመንድ ሊግ ለኢትዮጵያ አትሌቶች የተስፋ ሰጪ ውጤቶችን አስመዝግቧል።
ምንም እንኳን በ3,000 ሜትር የመድረክ ቦታ ማግኘት ባይቻልም፣ በርካታ አትሌቶች የግል ምርጥና የዓመቱን ምርጥ ሰዓት በማሻሻል ወደ ቀጣይ የዓለም ውድድሮች በጥሩ አቋም መግባታቸውን አሳይተዋል።

Facebooktwitterlinkedinyoutubetumblrinstagramflickrfoursquaremail
Facebooktwitterredditpinterestlinkedintumblrmail

By admin

Hello, dear. I am Wosenseged Mersha Demissie. Author, Journalist, and Sociological Criticism. He has worked in several media in Ethiopia and foreign media also. I have come to my country, Ethiopia, from abroad, and for the past eight years, I have been giving political analysis and writing in magazines, newspapers, and televisions on all the free press in Ethiopia. I have six books that I wrote and published during my stay abroad and after I came back to my country and are on the market. Above all, I feel spiritual satisfaction for coming from a developed country and working in a country where there is no freedom of the press. I have sacrificed a lot in this profession. Imprisonment, abuse—I was crushed economically. I have been living separately from my family for many years, but I am happy and proud of my career to be a voice for the voiceless people of Ethiopia, whom I love and respect by working in the press without payment. After leaving my country and returning to my country, Growing up in Arat Kilo, YMCA, I was exposed to various sports. I know many sports. I have worked as a referee, player, and tournament organizer. As a result, I have worked as a sports editor on radio, television, and newspapers for many years. I have worked alongside other media outlets for more than 20 years by preparing and publishing my own sports newspaper called San George.I have traveled to many countries, including Europe, the Far East, Asia, Oceania, and Africa, and have been present at many competitions, including athletics.This is because I have this love for sports. I have reopened this media outlet for sports. In addition to this, I have worked for the past 30 years. May God protect Ethiopia and its people and give peace and love to our world. Thank you anyway. Wosenseged Mersha Demissie Author, Journalist, Sociological Criticism

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *