የኢትዮጵያ ቴኳንዶ ፌዴሬሽን 4ኛ ጠቅላላ ጉባኤውን በአዲስ አበባ ከተማ አካሂዷል። ጉባኤው የኦዲትና የስራ ሪፖርቶችን መርምሮ በማጽደቅ፣ የ2019 በጀት ዓመት እቅድ ላይ ተወያቶ በማፅደቅ እና አዳዲስ የስራ አስፈፃሚ አባላትን በመምረጥ ተጠናቋል።

የፌዴሬሽኑ ፕሬዚዳንት ሳቦም አበራ ሚልኬሳ በጉባኤው መክፈቻ ባደረጉት ንግግር ፌዴሬሸኑ ባላፉት ዓመታት የቴኳንዶ ስፖርትን ለማስፋፋትና ለማሳደግ ለክልሎች እና ከተማ አስተዳደሮች ድጋፍ በማድረግ በዘረጋው የውድድር መርሀ ግብር በሀገር አቀፍ የክለቦች ሻምፒዮናዎችን፣ የግል እና የቡድን ውድድሮችን በዕድሜና ክብደት ደረጃ በማካሄድ ዉጤታማ ስራዎችን እንደሰራ አውሰተዋል።

በማከልም ሳቦም አበራ የኢትዮጵያ ቴኳንዶ ፌዴሬሽን ለአሰልጣኞች፣ ለዳኞች እና ለስፖርተኞች የሙያ ማሻሻያ እና የቴክኒክ ስልጠናዎችን በመስጠት አንድ ወጥ የአሰራር ደረጃ በመፍጠር በአህጉራዊና ዓለም አቀፍ ውድድሮች ሀገራቸውን የሚወክሉ ብሔራዊ የቴኳንዶ ቡድኖችን መምረጥና ማዘጋጀት እንደቻለ ገልፀዋል።

በጉባኤው የተሳተፉ አካላት በበኩላቸው ፌዴሬሸኑ በሚቀጥሉት ዓመታት ከሚመለከተው አካል ጋር በመተባበር የቴኳንዶ ስፖርት በሀገራችን በተዘረጋው የታዳጊ ወጣቶች የምዘናና የውድድር መርሀ ግብር ተካቶ ተተኪ ስፖርተኞች እንዲፈሩበት በትኩረት እንዲሰራ፣ የሀገር ውስጥ ውድድሮችን በማብዛት ዓለም አቀፍ የውድድር ተሳትፎን እንዲያሳድግ እና ፌዴሬሸኑን ገቢ የሚያሰስገኙ ፕሮጀክቶችን በመንደፍ እንዲሰራ ጠይቀዋል።

ጉባኤው ለሚቀጥሉት አራት ዓመታት የኢትዮጵያ ቴኳንዶ ፌዴሬሸንን የሚመሩ ስራ አሰፈፃሚዎችን ለመምረጥ የፌዴሬሸኑን ህግና ደንብ መሰረት በማድረግ በሰጠው ድምፅ ለሁለተኛ ዙር ሳቦም አበራ ሚልኬሳን በፕሬዚዳንትነት በሙሉ ድምፅ ሲመርጥ በስራ አስፈፃሚነት አቶ ከድር አህመድ፣ አቶ ተገኑ በቀለ፣ አቶ መኪ ገመቹ ፣ ወ/ሮ አስቴር ደርበው፣ ወ/ሮ ማዓዛ ጋሻው እና ወ/ሮ በዓል ግርማቸውን መርጧል።

ተመራጮቹም ጉባዔው እምነት ጥሎ ለሰጣቸው ድምፅ በመታመን ለስፖርቱ እድገት እንደሚሰሩ ቃል ገብተዋል።

በመጨረሻም የኢፌዴሪ ባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ተወካይ አቶ ከበደ እጅጉ 4ኛ ጠቅላላ ጉባኤውን ያካሄደው የኢትዮጵያ ቴኳንዶ ፌዴሬሸን እንደ ሃገር የሚያከናውናቸው ማሕበራዊ አበርክቶዎች የሚደነቅ መሆኑን በመግለፅ በዛሬው እለት ያካሄደው ጉባኤም በጉባዔተኞች የነቃ ተሳትፎ የደመቀ በዲሞክራሲያዊ መንገድ ምርጫ የተደረገበት መሆኑን ተናግረው ፌዴሬሽኑ በቀጣይ የሚያከናውናቸው ተግባራት በስትራቴጅክ እቅድ ተደግፈው ጉባኤተኛው ያነሳቸው ሀሳቦች በግበዓትነት ተይዘው የሚተገበሩ እንዲሆኑ አሳስበዋል።

Facebooktwitterlinkedinyoutubetumblrinstagramflickrfoursquaremail
Facebooktwitterredditpinterestlinkedintumblrmail

By admin

Hello, dear. I am Wosenseged Mersha Demissie. Author, Journalist, and Sociological Criticism. He has worked in several media in Ethiopia and foreign media also. I have come to my country, Ethiopia, from abroad, and for the past eight years, I have been giving political analysis and writing in magazines, newspapers, and televisions on all the free press in Ethiopia. I have six books that I wrote and published during my stay abroad and after I came back to my country and are on the market. Above all, I feel spiritual satisfaction for coming from a developed country and working in a country where there is no freedom of the press. I have sacrificed a lot in this profession. Imprisonment, abuse—I was crushed economically. I have been living separately from my family for many years, but I am happy and proud of my career to be a voice for the voiceless people of Ethiopia, whom I love and respect by working in the press without payment. After leaving my country and returning to my country, Growing up in Arat Kilo, YMCA, I was exposed to various sports. I know many sports. I have worked as a referee, player, and tournament organizer. As a result, I have worked as a sports editor on radio, television, and newspapers for many years. I have worked alongside other media outlets for more than 20 years by preparing and publishing my own sports newspaper called San George.I have traveled to many countries, including Europe, the Far East, Asia, Oceania, and Africa, and have been present at many competitions, including athletics.This is because I have this love for sports. I have reopened this media outlet for sports. In addition to this, I have worked for the past 30 years. May God protect Ethiopia and its people and give peace and love to our world. Thank you anyway. Wosenseged Mersha Demissie Author, Journalist, Sociological Criticism

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *